“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው”

------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

(ዜና ፓርላማ) ታህሳስ 08 ፣ 2018 ዓ.ም፤ የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ፣ ዛሬ በሕዝብ ተወካዮች እና በፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ ላይ በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።

በመልዕክታቸው ሁለቱ የጥንታዊ ሥልጣኔ ባለቤት አገራት መካከል ያለው ግንኙነት ወደ ስትራቴጂክ አጋርነትና አዲስ ምዕራፍ የተሸጋገረበት ወቅት ላይ እንገኛለን ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት ሁለቱ አገራት በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ዲፕሎማሲያዊ ዘርፎች ያላቸው ግንኙነት ማደጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ሕንዳውያን ባለሀብቶች በጤና፣ በግብርና እና አምራች ዘርፎች ከ 5 ቢሊየን ዶላር በላይ ኢንቨስት በማድረግ ላይ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

ሁለቱ አገራት በያሉበት አህጉር ተፅህኖ ፈጣሪ መሆናቸውን ገልጸው ለጋራ ተጠቃሚነትና ብልፅግና በስትራቴጂካዊ ትብብር በጋራ እንሰራለን ብለዋል።

ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገር እንድትሆን ሕንድ ድጋፍ ማድረጓንም ጠቁመዋል።

በርካታ ኢትዮጵያዊያን በሕንድ የትምሀርት ዕድል አግኝተዋል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአየር ንብረት ለውጥ በመከላከል፣ በጤና በግብርና፣ በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ በጋራ ለመሥራት ዝግጁ ነን ብለዋል።

አዲስ ሐሳቦችን ለሚያፈልቁ የሥራ ፈጣሪ ወጣቶችና ተቋማትን መገንባትና ማበረታታት የኢትዮጵያን መጪ ዘመናት የሚቀይርና የሚወስን ነው ሲሉም ተናግረዋል።

በዚህ ታላቅ ምክር ቤት ውስጥ ሕጎቻችሁ ይወጣሉ፤ እዚህ ውስጥ የሕዝቡ መሻት የመንግሥት መሻት ይሆናል ያሉ ሲሆን በውይይትና ዲሞክራሲያዊ መንገድ የህግ የበላይነትን ማክበር ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለተደረገላቸው የክብር አቀባበልና ለተበረከተላቸው የኢትዮጵያ ታላቁ የክብር ኒሻን ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አመስግነዋል።

(በ በለጠ ሙሉጌታ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 


ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

ተያያዥ ዜናዎች

Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እና ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጠጣመ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

ተጨማሪ ለማንበብ...