ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 03፣ 2017 ዓ.ም.፤ ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቷል፡፡ ረቂቅ በጀቱን በተመለከተ የበጀት መግለጫውን የገንዘብ ሚኒሰትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ለምክር ቤት አባላት አቅርበዋል፡፡ ረቂቅ በጀቱ ለምክር ቤቱ 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ የቀረበ ሲሆን፣ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 4 መቶ 15 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 3 መቶ 15 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ እንደሚውል ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል፡፡ የ2018 በጀት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠል፣ ማሕበራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣ የዕዳ ስረዛን ወደ መካከለኛ ደረጃ ለማውረድ እና ማክሮ ኢኮኖሚውን ማረጋጋት ላይ ያተኮረ እንደሚሆን ነው ያብራሩት፡፡ እንዲሁም፣ የመንግስትን የገቢ አሰባሰብ ለማሳደግ፣ የክልል መንግስታት ገቢን ለማሳደግ እና የታክስ አስተዳደርን ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ክቡር አቶ አህመድ አብራርተዋል፡፡ ረቂቅ በጀቱ የ10 ዓመቱን መሪ የልማት እቅድን እና የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንደተዘጋጀ ጨምረው አብራርተዋል፡፡ በካፒታል በጀቱ መንገዶችን እና ትምህርትን ለማስፋፋት፣ መስኖና የግብርና ስራዎችን ለማዘመን፣ የገጠር እና ከተማ ምግብ ዋስትና እና ልማታዊ ሴፍቲኔትን ለማረጋገጥ እንደሚውል ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡ እንዲሁም፣ በጀቱ የጤናውን ዘርፍ ለማስፋት፣ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች መልሶ ለመቋቋም ፣ ለመንግስት ቢሮ ግንባታ እና ለንጹህ መጠጥ ውሃ እንደሚውል ነው አቶ አህመድ ያስረዱት፡፡ በ2018 በጀት ዓመት የ8 ነጥብ 9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት እንደሚመዘገብ መተንበይ መቻሉን ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ተያያዥ ዜናዎች

Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እና ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጠጣመ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

ተጨማሪ ለማንበብ...