"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

(ዜና ፓርላማ) ግንቦት 28፣ 2017 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 34ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን፤ ኤርትራን ጨምሮ ከተለያዩ የጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት፣ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን መብት ለማስጠበቅና ከተለያዩ አደጋዎች ለመታደግ የሚደረገው ጥረት፣ በድንበር አከባቢ የሚሰፍሩ የጎረቤት ሀገራት ህዝቦች እና በውጭ ኃይሎች የተያዙ የኢትዮጵያ ግዛቶችን በሚመለከት የተነሱት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ኢትዮጳያ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ዲፕሎማሲያዊ መርህ እንዳላት ጠቁመው፤ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከተለዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር የሚሰራው ስራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት እንዲረጋገጥ ለቀጣናው ኢኮኖሚ ትስስር መጠናከር ወሳኝ ሚና የምትጫወት ሀገር ስለመሆኗ በተለያዩ አለም አቀፍ መድረኮች እየተረጋገጠ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ ጋር የቃላት ጦርነት ውስጥ አለመግባቱንና የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ እውን እስኪሆን ድረስ በዓለም አቀፍ ህጎች እና በሰጥቶ መቀበል መርህ መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል። በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ያለው ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከመንግስታት ግንኙነት የላቀ ትርጉም ያለው በመሆኑ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጌዲዮን (ዶ/ር) አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፣ በህጋዊ መንገድ በውጭ ሀገራት የሚሰሩ ዜጎችን መብት በማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸው፤ ነገር ግን በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የመውጣቱ ጉዳይ አሁንም ፈታኝ እንደሆነባቸው አስረድተዋል፡፡

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ተያያዥ ዜናዎች

Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እና ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጠጣመ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

ተጨማሪ ለማንበብ...