(ዜና ፓርላማ) ግንቦት 28፣ 2017 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 34ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን፤ ኤርትራን ጨምሮ ከተለያዩ የጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት፣ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን መብት ለማስጠበቅና ከተለያዩ አደጋዎች ለመታደግ የሚደረገው ጥረት፣ በድንበር አከባቢ የሚሰፍሩ የጎረቤት ሀገራት ህዝቦች እና በውጭ ኃይሎች የተያዙ የኢትዮጵያ ግዛቶችን በሚመለከት የተነሱት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ኢትዮጳያ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ዲፕሎማሲያዊ መርህ እንዳላት ጠቁመው፤ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከተለዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር የሚሰራው ስራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት እንዲረጋገጥ ለቀጣናው ኢኮኖሚ ትስስር መጠናከር ወሳኝ ሚና የምትጫወት ሀገር ስለመሆኗ በተለያዩ አለም አቀፍ መድረኮች እየተረጋገጠ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ ጋር የቃላት ጦርነት ውስጥ አለመግባቱንና የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ እውን እስኪሆን ድረስ በዓለም አቀፍ ህጎች እና በሰጥቶ መቀበል መርህ መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል።
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ያለው ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከመንግስታት ግንኙነት የላቀ ትርጉም ያለው በመሆኑ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጌዲዮን (ዶ/ር) አንስተዋል፡፡
በሌላ በኩል በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፣ በህጋዊ መንገድ በውጭ ሀገራት የሚሰሩ ዜጎችን መብት በማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸው፤ ነገር ግን በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የመውጣቱ ጉዳይ አሁንም ፈታኝ እንደሆነባቸው አስረድተዋል፡፡
- መነሻ ገጽ
-
ያግኙን
ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።እባኮትን ይህንን ቅጽ ይሙሉ እና የፓርላማ ጉብኝት መርሃ ግብር ለማዘጋጀት ያቅርቡፕሮስፔክተስ በቀላሉ መረጃ መስጠት ነው። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቁጥጥር እና የቁጥጥር ስልጣኑን ተግባራዊ ለማድረግ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት መረጃ የመሰብሰብ ስልቶችን አስቀምጧል።ምክር ቤቱ በአንቀጽ 55፣ አንቀጽ 70(1)፣ አንቀጽ 79(4)(ሐ)፣ አንቀጽ 82(2)(ሐ)፣ አንቀጽ 101፣ አንቀጽ 102፣ አንቀጽ 103 እና... የተሰጡት ሥልጣንና ተግባራት ይኖሩታል።የምክር ቤቱ የአሰራርና የአባላት ሥነ ምግባር ቁጥር 6/2008 አንቀጽ 105 የሹመት ዓይነቶች በሦስት የተከፈሉ መሆናቸውን ያመለክታል።
-
ስብሰባዎች እና ዝግጅቶች
ቀጣይ መርሓ ግብሮች
አዲስ መረሓ ግብር የለም -
የእውቀት መረጃዎች
የኢ.ፌ.ድ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት
ተጨማሪ ለማንበብ...የኢትዮጵያ ፓርላማ የተቋቋመው በህዳር 3 ቀን 1931 ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በሐምሌ ወር 1931 የመጀመሪያውን ሕገ መንግሥት ካወጁ በኋላ ነው። እንደዚያም ሆኖ አሠራሩ እንደየአገዛዙ ይለያያል። ይህ ጽሑፍ በ... የገቡትን ፓርላማዎች ምንነት ለማቅረብ ይሞክራል።
የኢ.ፌ.ድ.ሪ መርጃዎችን ያግኙ