የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

-----------------

(ዜና ፓርላማ) ታህሳስ 14 2018 .ም፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5 ዓመት የሥራ ዘመኑ 5 መደበኛ ሥብሰባው የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን መርምሮ አፅድቋል::  

 የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ ቋሚ ኮሚቴው ያዘጋጃውን ሪፖርትና የውሳኔ ሃሳብ ያቀረቡ ሲሆን ረቂቅ አዋጁ ከጊዜ ወደ ጊዜ በፍጥነት እየተሻሻሉና እየተለወጡ የመጡትን ዓለም አቀፋዊ የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንቲን ደረጃዎችና አሰራሮች በመከተል ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጋር የተናበበ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ሥራ ለመስራት መደላድል የሚፈጥር መሆኑን አንስተዋል:: 

የተከበሩ አቶ ሰለሞን አያይዘውም አግባብነት ያለውና ደረጃውን የጠበቀ የተባይ አሰሳና ቅኝት ሥጋት ትንተና ለማድረግ እና በመግቢያ በሮች የገቢና ወጭ እፅዋት የእፅዋት ውጤት እና ሌሎች ቁጥጥር የሚደረግባቸው ቁሶችን በተገቢው ለመቆጣጠር የሚያስችል ማዕቀፍ ያለው መሆኑን እንዲሁም ዘመናዊ የተባይ መከላከል እና መቆጣጠር ሥርዓትን በመዘርጋት ምርታማነትንና የምርት ጥራትን በማሳደግ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን አስረድተዋል። 

ፈቃድ ሳያወጡ ወይም ህጋዊ ባልሆነ መንገድ  በአየር እና በየብስ ከእፅዋትና የእፅዋት ውጤቶች ጋር የሚገቡ ተባዮችን ለመከላከል አዋጁ ያስቀመጠው  የመከላከያ መንገድ  ስለመኖሩ፣ ከእፅዋትና ከእፅዋት ውጤቶች ጋር ተባዮች ብቻ ሳይሆኑ አረሞችም የሚገቡበት ሁኔታ ስላለ ተባይ በሚል ብቻ የተቀመጠበትን ምክንያት በተመለከተ እንዲሁም ሌሎች በርካታ ጥያቄዎች ከምክር ቤት አባላት የተነሱ  ሲሆን በግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሰቢ በተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል:: 

ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን አዋጅ ቁጥር 1420/ 2018 በማድረግ  በሙሉ ድምጽ አፅድቆታል። 

ምክር ቤቱ 4 ዓመት የስራ ዘመኑ ሰኔ 5 ቀን፣ 2017 . ባካሄደው 36 መደበኛ ስብሰባ የእፅዎት ጥበቃ እና ኳላንታይን ረቂቅ አዋጅን ለዝርዝር እይታ ለግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መምራቱ ይታወሳል።

   (በፀሀይ ነጋሽ)

 

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።


ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

ተያያዥ ዜናዎች

Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

ምክር ቤቱ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

"የባህር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው"

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

"ወጣቶች የሀገራችን የነገ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች ናቸው"

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

ተጨማሪ ለማንበብ...