(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 10 ቀን፣ 2017 ዓ.ም፤ ምክር ቤቱ ባካሄደው ጉባኤ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቷል።
ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ የመንግሰት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡
በማብራሪያቸውም ረቂቅ አዋጁ ኢኖቬሽን ነባር አሠራሮችን፣ የምርትና የአገልግሎት ሂደቶችንና ምርቶችን በሳይንሳዊ መንገድ በመቀየር ሰዎች ሕይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩ የሚያደርግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሀገራት ይህን ከባቢያዊ ሥርዓት ለመፍጠር የሚያስችሉ ሕጎች ማውጣታቸውን እና በዚህ ዘርፍ ከተሰማሩ ከሃሳብ አፍላቂዎች ጀምሮ መዋዕለ ንዋያቸውን ኢንቨስት ላደረጉና ለሚያደርጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች የአገራቱ አቅም የሚፈቅደውን እና ተገቢ ነው ያሉትን የማበረታቻ ማዕቀፍ አዘጋጅተው ወደ ሥራ ማስገባታቸውንም አብራርተዋል፡፡
በአገራችን ኢትዮጵያ ይህን ሥርዓት መፍጠር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂን ከማስረጽና በኢኮኖሚው ውስጥ ሊያመጣ የሚችለውን አዎንታዊ ውጤት የሚመጣ፣ በተለይም ለወጣቶች የሥራ ዕድል የመፍጠር አቅሙም ከፍተኛ የሆነ እንዲሁም በአገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ለውጥ ታሳቢ በማድረግ የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር አስፈላጊ መሆኑንም ነው የተከበሩ ተስፋዬ በልጅጌ (ዶ/ር) የገለጹት።
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው ረቂቅ አዋጁ ሀሳብን ወደ ገንዘብ የሚቀየርበትን መንገድ የሚፈጥር እና ፈጠራን የሚያበረታታ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በስፋት ከተወያየበት በኋላ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 2320/2017 ሆኖ ለዝርዝር ዕይታ ለሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምጽ መርቷል፡፡
- Home
-
Contact Us
The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Please complete this form and submit it to schedule a parliamentary visit.A prospectus is simply a means of providing information. The House of People's Representatives has put in place mechanisms to collect information from various stakeholders to exercise its oversight and regulatory powers.The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Article 105 of the Council's Code of Conduct and Ethics No. 6/2008 indicates that the types of appointments are divided into three categories.
-
Meetings & Events
Upcoming Events
No new events -
Information of knowledge
House of People's Representatives of the Federal Democratic Republic of Ethiopia
Read MoreThe Ethiopian Parliament was established on November 3, 1931, after Emperor Haile Selassie I promulgated the first constitution in July 1931. However, its functioning varies from regime to regime. This article attempts to present the nature of the parliaments that have been established in...