(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 03፣ 2017 ዓ.ም.፤ ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያይቷል፡፡
ረቂቅ በጀቱን በተመለከተ የበጀት መግለጫውን የገንዘብ ሚኒሰትሩ ክቡር አቶ አህመድ ሽዴ ለምክር ቤት አባላት አቅርበዋል፡፡
ረቂቅ በጀቱ ለምክር ቤቱ 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ሆኖ የቀረበ ሲሆን፣ 1 ነጥብ 2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ፣ 4 መቶ 15 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ፣ 3 መቶ 15 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት ድጋፍ እንዲሁም 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለክልሎች የዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈፀሚያ ድጋፍ እንደሚውል ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል፡፡
የ2018 በጀት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ለማስቀጠል፣ ማሕበራዊ ወጪዎችን ለመሸፈን፣ የዕዳ ስረዛን ወደ መካከለኛ ደረጃ ለማውረድ እና ማክሮ ኢኮኖሚውን ማረጋጋት ላይ ያተኮረ እንደሚሆን ነው ያብራሩት፡፡
እንዲሁም፣ የመንግስትን የገቢ አሰባሰብ ለማሳደግ፣ የክልል መንግስታት ገቢን ለማሳደግ እና የታክስ አስተዳደርን ለማጠናከር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ክቡር አቶ አህመድ አብራርተዋል፡፡
ረቂቅ በጀቱ የ10 ዓመቱን መሪ የልማት እቅድን እና የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንደተዘጋጀ ጨምረው አብራርተዋል፡፡
በካፒታል በጀቱ መንገዶችን እና ትምህርትን ለማስፋፋት፣ መስኖና የግብርና ስራዎችን ለማዘመን፣ የገጠር እና ከተማ ምግብ ዋስትና እና ልማታዊ ሴፍቲኔትን ለማረጋገጥ እንደሚውል ሚኒስትሩ አብራርተዋል፡፡
እንዲሁም፣ በጀቱ የጤናውን ዘርፍ ለማስፋት፣ በጦርነቱ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች መልሶ ለመቋቋም ፣ ለመንግስት ቢሮ ግንባታ እና ለንጹህ መጠጥ ውሃ እንደሚውል ነው አቶ አህመድ ያስረዱት፡፡
በ2018 በጀት ዓመት የ8 ነጥብ 9 በመቶ የኢኮኖሚ እድገት እንደሚመዘገብ መተንበይ መቻሉን ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
- Home
-
Contact Us
The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Please complete this form and submit it to schedule a parliamentary visit.A prospectus is simply a means of providing information. The House of People's Representatives has put in place mechanisms to collect information from various stakeholders to exercise its oversight and regulatory powers.The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Article 105 of the Council's Code of Conduct and Ethics No. 6/2008 indicates that the types of appointments are divided into three categories.
-
Meetings & Events
Upcoming Events
No new events -
Information of knowledge
House of People's Representatives of the Federal Democratic Republic of Ethiopia
Read MoreThe Ethiopian Parliament was established on November 3, 1931, after Emperor Haile Selassie I promulgated the first constitution in July 1931. However, its functioning varies from regime to regime. This article attempts to present the nature of the parliaments that have been established in...