(ዜና ፓርላማ) ግንቦት 28፣ 2017 ዓ.ም፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡
ዛሬ በተካሄደው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 34ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
የምክር ቤቱ አባላት የተለያዩ ጥያቄዎች ላይ ማብራሪያ የጠየቁ ሲሆን፤ ኤርትራን ጨምሮ ከተለያዩ የጎረቤት ሀገራት ጋር ያለው ግንኙነት፣ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንን መብት ለማስጠበቅና ከተለያዩ አደጋዎች ለመታደግ የሚደረገው ጥረት፣ በድንበር አከባቢ የሚሰፍሩ የጎረቤት ሀገራት ህዝቦች እና በውጭ ኃይሎች የተያዙ የኢትዮጵያ ግዛቶችን በሚመለከት የተነሱት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ኢትዮጳያ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ዲፕሎማሲያዊ መርህ እንዳላት ጠቁመው፤ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከተለዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር የሚሰራው ስራም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና መረጋጋት እንዲረጋገጥ ለቀጣናው ኢኮኖሚ ትስስር መጠናከር ወሳኝ ሚና የምትጫወት ሀገር ስለመሆኗ በተለያዩ አለም አቀፍ መድረኮች እየተረጋገጠ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ ጋር የቃላት ጦርነት ውስጥ አለመግባቱንና የባህር በር ጥያቄን ለማሳካት የተጀመረው ዲፕሎማሲያዊ አካሄድ እውን እስኪሆን ድረስ በዓለም አቀፍ ህጎች እና በሰጥቶ መቀበል መርህ መስራት እንደሚገባም አመላክተዋል።
በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ያለው ህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ከመንግስታት ግንኙነት የላቀ ትርጉም ያለው በመሆኑ በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጌዲዮን (ዶ/ር) አንስተዋል፡፡
በሌላ በኩል በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የሚወጡ ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት በመመለስ፣ በህጋዊ መንገድ በውጭ ሀገራት የሚሰሩ ዜጎችን መብት በማስጠበቅ እየተሰሩ ያሉት ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገልጸው፤ ነገር ግን በህገ ወጥ መንገድ ከሀገር የመውጣቱ ጉዳይ አሁንም ፈታኝ እንደሆነባቸው አስረድተዋል፡፡
- Home
-
Contact Us
The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Please complete this form and submit it to schedule a parliamentary visit.A prospectus is simply a means of providing information. The House of People's Representatives has put in place mechanisms to collect information from various stakeholders to exercise its oversight and regulatory powers.The HOPR shall have the powers and functions conferred on it by Article 55, Article 70(1), Article 79(4)(c), Article 82(2)(c), Article 101, Article 102, Article 103 and...Article 105 of the Council's Code of Conduct and Ethics No. 6/2008 indicates that the types of appointments are divided into three categories.
-
Meetings & Events
Upcoming Events
No new events -
Information of knowledge
House of People's Representatives of the Federal Democratic Republic of Ethiopia
Read MoreThe Ethiopian Parliament was established on November 3, 1931, after Emperor Haile Selassie I promulgated the first constitution in July 1931. However, its functioning varies from regime to regime. This article attempts to present the nature of the parliaments that have been established in...