አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

(ዜና ፓርላማ)  ሐምሌ 10፣ 2017 ዓ.ም፤ የስታርታፕ አዋጅ ለወጣቶችና ታዳጊዎች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊና የቴክኖሎጂ እድገት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳለው የኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ገልጸዋል።

ይህ የተገለጸው ምክር ቤቱ ባካሄደው 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ሲሆን፣ የሃገርን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማጎልበት እና ለወጣቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል ከመፍጠር አኳያ አዳዲስ የሀብት ምንጭ የሆኑ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤቶችን ለማበረታታት አዋጁ እንደሚያግዝ አባላቱ ተናግረዋል።

የስታርታፕ ፕሮግራም የተለያዩ የአስፈጻሚ ተቋማት፣ የፋይናንስ ድርጅቶችን እንዲሁም ባለሀብቶችን በማጣመርና በማስተሳሰር ምቹ የሆነ የኢኮኖሚ ስነ-ምህዳር መፍጠር የሚያስችል እንደሆነም አባላቱ ተናግረዋል፡፡

በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁን ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ በዓለም አቀፍ ደረጃ በኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ የተደገፈ የስታርታፕ ውጤት በሂደት ትላልቅ ኢንዱስትሪዎችንና ኩባንያዎችን በማፍራት ለኢኮኖሚ ዕድገትና ልማት  ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት አብራርተዋል።

ሰብሳቢው ስታርታፕ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የኢኮኖሚ ዕድገትና ልማትን ለማፋጠን ቁልፍ ሚና ያለውና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እንድትሆን የሚያስችል ነው ብለዋል ።

አዋጁ ምቹ የስታርታፕ ምህዳርን በመገንባት ስታርታፖችን ውጤታማና ስኬታማ በማድረግ፤ ስታርታፖች እና የስታርታፕ ምህዳር ገንቢዎችን ዒላማ ያደረገ የተቀናጀ ድጋፍ መስጠት የሚያስችል የተሳለጠ የስያሜ፣ የዕውቅና እና የአቅም ግንባታ አተገባበር ሥርዓት በመዘርጋት ቀጣይነት ያለው የቴክኖሎጂና የኢኮኖሚ እምርታን እንደሚያረጋግጥ ተናግረዋል።

ስታርታፖችን እና የስፓርታፕ ምህዳር ገንቢዎች የሚያጋጥማቸውን የፋይናንስ አቅርቦት ተግዳሮቶች እና የፋይናንስ ስጋትን በዘላቂነት ለመቅረፍ የግራንት ፕሮግራም፣ የብድር ዋስትና ማዕቀፍ እና የፈንዶች ፈንድ መዋቅር ማደራጀት የሚያስችል አዋጅ እንደሆነም ሰብሳቢው ገልጸዋል። ምክር ቤቱም አዋጁን መርምሮ በሙሉ ድምጽ አፅድቋል፡፡


ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

Related News

Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

አዋጁ ሽብርተኝነትንና ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል እና ከዓለም አቀፍ ህጎች ጋር የተጠጣመ መሆኑ ተገለጸ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ በፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ ተወያየ

Read More