"ወጣቶች የሀገራችን የነገ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች ናቸው"

"ወጣቶች የሀገራችን የነገ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች ናቸው"

"ወጣቶች የሀገራችን የነገ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች ናቸው"

       ------ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ ----

(ዜና ፓርላማ) ታህሳስ 14፣ 2018 ዓ.ም፤ በኢትዮጵያ የሚገኙ አፍላ-ወጣቶችና ወጣቶች የሀገሪቱ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች  ናቸው ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባዔ  የተከበሩ ወ/ሮሎሚ በዶ ገለጹ።

ወጣቶች በቀጣይ ሀገር ተረካቢ ዜጎች መሆናቸውን መንግሥት በጽኑ በማመን ከወዲሁ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሆነም  የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ  አስገንዝበዋል።

አፈ-ጉባኤዋ ይህንን ያሉት "Harnessing the Population Dividend by Investing in Ethiopia Youth” በሚል ርዕስ ላይ በአ..ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፥ በዲ.ኤስ.ደብሊው (DSW) ኢትዮጵያ እና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን ጋር  የምክክር መድረክ በተካሄደበት  ወቅት ነው።

ወጣቶች በትምህርት፣ በሥራ ዕድል እና በሌሎች ተጓዳኝ አገልግሎቶች የሚደገፉ ከሆነ ለሀገር ሁለንተናዊ እድገትና ብልጽግና እንዲሁም ለዘላቂ ልማት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከት ይችላሉ ሲሉ አፈ-ጉባዔዋ ገልጸዋል።

ወጣቶች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች የመፍጠርና የመቀበል እንዲሁም አዳዲስ ሀሳቦችን በማመንጨት የመፍትሔ ሐሳብም የሚያመጡ በመሆኑ ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ትልቅ የለውጥ ዕድል መሆን ይችላሉ ብለዋል።

በምክር ቤቱ የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባሕልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የተከበሩ ወርቀሰሙ ማሞ በበኩላቸው፤  ወጣቶችና አፍላ ወጣቶች የሀገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ የላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አመላክተዋል።

ወጣቶች በኢትዮጵያ ማህበራዊ፣ ምጣኔ ሀብታዊ እና ፖሊቲካዊ ጉዳዮች ላይ የሚያደርጉትን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ለማሳደግ  የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን መፍጠር እንደሚያስፈልግም የተከበሩ ወ/ሮ ወርቅሰሙ  አስረድተዋል።

በምክክር መድረኩ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የዲ.ኤስ.ደብሊው (DSW) ኢትዮጵያ የስራ ሀላፊዎች የተገኙ ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምሁራን በወጣቶች ዙሪያ የተሰሩ የተለያዩ ጥናታዊ ጹሁፎችን እያቀረቡ ይገኛሉ።

(በሚፍታህ ኪያር)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም  https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር  http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 


ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

Related News

Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

ምክር ቤቱ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

"የባህር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው"

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

ምክር ቤቱ አቶ ተስፋዬ ንዋይን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አድርጎ ሾመ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

"የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ ከጎረቤት ሀገራት ብቻ ሳይሆን ከተለያዩ ቀጠናዊ ኃይሎች ጋር በጋራ እንሰራለን": - ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር)

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ ነሐሴ 16, 2017

አዋጁ ለወጣቶች ከፍተኛ የስራ እድል በመፍጠር የሀገራችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ

Read More
Marta Lorenzo from UNRWA

ቅዳሜ ግንቦት 30, 2017

ምክር ቤቱ የስታርትአፕ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መራ

Read More