አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖችን አፅናኑ
--------------------
(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 04፣ 2018 ዓ.ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖችን አፅናንተዋል።
ዋና አፈ ጉባኤው በትላንትናው ዕለት የኩልፎ ወንዝ ሙላት በአርባ ምንጭ ከተማ በንብረት እና መሠረተ ልማት ላይ ያደረሰውን ጉዳት ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን፣ በዛሬው ዕለት ደግሞ ለማፅናኛ በተዘጋጀ ስፍራ በመገኘት የተጎጂ ቤተሰቦችን አፅናንተዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደን ጨምሮ የክልል፣ የጋሞ ዞን እና የአርባምንጭ ከተማ አሰተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በስፍራው ተገኝተዋል።
በጋሞ ዞን 4 ወረዳዎች በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ አስከአሁን 70 ሰዎች መሞታቸው ተገልጿል።
የአስክሬን ፍለጋው በሂደት ላይ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል ይገመታል።
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
በትዊተር
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።