የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ዜጎች የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
------------------------
(ዜና ፓርላማ) መጋቢት 25፣ 2018 ዓ.ም፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ ሳቢያ ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ10 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።
የምክር ቤቱ ምክትል አፈ-ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶን ጨምሮ፣ የመንግስት ተጠሪ ሚኒስትር፣ የምክር ቤት አባላትና የጽሕፈት ቤት የሥራ ኃላፊዎች በዞኑ በአካል ተገኝተው የምክር ቤቱን አጋርነት አሳይተዋል።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ሎሚ በዶ፤ በዞኑ በተከሰተው አደጋ ምክንያት በወገኖቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ ማዘናቸውን ገልፀው ለተጎጂ ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።
ምክር ቤቱ ያለውን አጋርነት ለማሳየትም የ10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ለጋሞ ዞን አስተዳደር ያስረከቡ ሲሆን ዜጎቸን በዘላቂነት ለማቋቋም በሚደረገው ተግባር ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡
የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደምስ አድማሱ (ዶ/ር) ምክር ቤቱ ላሳየው ፈጣን ምላሽና አጋርነት በዞኑ ሕዝብና በአስተዳደሩ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ድጋፎች የተረጂዎችን ሞራል ከመገንባት ባለፈ፣ መልሶ የማቋቋም ሥራውን እንደሚያቀላጥፉ ጠቁመዋል።
(በ አገሪቱ ጌቴ)
ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament
በዩቲዩብ
https://www.youtube.com/@FDREHOPR
በቴሌግራም
በትዊተር
በዌብሳይት
www.hopr.gov.et ይከታተሉ።