ረቂቅ አዋጁ በአቬሽን ደህንነት ረገድ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገለጸ

ረቂቅ አዋጁ በአቬሽን ደህንነት ረገድ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገለጸ

ረቂቅ አዋጁ በአቬሽን ደህንነት ረገድ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጥ መሆኑ ተገለጸ

---------------------

(ዜና ፓርላማ) የካቲት 10 2018 . የኢትዮጵያ የአቬሽን ሴኪዩሪቲ ረቂቅ አዋጅ በአቬሽን ደህንነት ረገድ የኢትዮጵያን ከፍታ የሚያረጋግጥ መሆኑን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አስንዝቧል፡፡

ቋሚ ኮሚቴው በኢትዮጵያ የአቬሽን ሴኪዩሪቲ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል፡፡

ረቂቅ አዋጁ ቀደም ሲል በዋናነት ለውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እና በተባባሪነት ለከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለዝርዝር እይታ መመራቱ ይታወሳል፡፡

በውይይቱም ከባለድርሻ አካላት ግልጽነት ያስፈልጋቸዋል የተባሉ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነስተው በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የስራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡

የከተማ መሰረተ-ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የተከበሩ ፕሮፌሰር መሀመድ አብዶ በሰጡት አስተያየት ረቂቅ አዋጁ በአቬሽን ደህንነት ዘርፍ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደረጃ ከፍ በማድረግ ረገድ ፋይዳው ከፍተኛ ስለሆነ ግልፅነት የጎደላቸውን ቃላት በማስተካከል ጸድቆ ወደ ተግባር እንዲገባ ጥረት መደረግ አለበት ብለዋል፡፡

የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈቲህ መሀዲ (/) በበኩላቸው አዋጁ በጥራቱና በቅልጥፍናው የአቬሽን ደህንነትን የበለጠ የሚያጠናክር እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አለም አቀፍ የአቬሽን ደህንነት መመዘኛን በማሟላት ቀዳሚ ሆኖ እንዲቀጥል ያስችላል ብለዋል፡፡

የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሲሳይ ቶላ በበኩላቸው በአየር ትራንስፖርት ስርዓቱ የሚቃጡ የሕገ-ወጥ ድርጊቶች ባህሪያትና የአፈፃፀም ስልት ከግዜ ወደ ግዜ እያደገና እየተወሳሰበ በመምጣቱ የአቭዬሽን ደህንነት ስጋቶችን በብቃትና በጥራት መከላከል እንዲያስችል ቀደም ሲል የነበረው የአቭዬሽን ሴኩዩሪቲ አዋጅ ቁጥር 432/1997 ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል ብለዋል።

(በድረስ ገብሬ)

ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

በፌስቡክ http://www.facebook.com/hoprparliament

በዩቲዩብ

https://www.youtube.com/@FDREHOPR

በቴሌግራም

https://t.me/ParlamaNews

በትዊተር

http://twitter.com/fdrehopr

በዌብሳይት

www.hopr.gov.et ይከታተሉ።

 


ማክሰኞ የካቲት 10, 2018

ተያያዥ ዜናዎች

Marta Lorenzo from UNRWA

ዓርብ መጋቢት 04, 2018

አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ በጋሞ ዞን በመሬት መንሸራተት አደጋ የተጎዱ ወገኖችን አፅናኑ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ የካቲት 24, 2018

"ነፃ፣ ገለልተኛና ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ለተሳካ ሀገረ መንግሥት ግንባታ የላቀ ሚና አለው "

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሰኞ የካቲት 09, 2018

የስፖርቱ ዘርፍ ለሀገር ኢኮኖሚና ለትውልድ ቅብብሎሽ ያለውን አበርክቶ ለማሳደግ በህግና ስርዓት ሊመራ እንደሚገባ ተገለፀ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

ምክር ቤቱ የሥርዓተ ምህዳር አገልግሎት ክፍያ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 21, 2018

"የባህር በር ባለቤትነት የትውልድ ጥያቄ ነው"

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

"ወጣቶች የሀገራችን የነገ ተሰፋዎች ብቻ ሣይሆኑ የዛሬም የልማት ሞተሮች ናቸው"

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ማክሰኞ ታኅሣሥ 14, 2018

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የእፅዋት ጥበቃ እና ኳራንታይን ረቂቅ አዋጅን አፀደቀ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ህንድ መካከል ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት በተለያዩ ዘርፎች አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል“ ---- አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ረቡዕ ታኅሣሥ 08, 2018

“በኢትዮጵያ እና ሕንድ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት አዲስ ምዕራፍ የተከፈተበት ወቅት ነው” ‎ ------ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ------

ተጨማሪ ለማንበብ...
Marta Lorenzo from UNRWA

ሓሙስ ታኅሣሥ 02, 2018

በሀገራዊ የልማት ፕሮጀክቶች የክዋኔ ኦዲት የተገኙ ክፍተቶች እንዲታረሙ ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

ተጨማሪ ለማንበብ...